Wednesday, August 29, 2012

በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ምክር ያቋቋሟቸውን ኩባንያዎች ስራ አስፍቼ ቀጥላለሁ አሉ ሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ

Wednesday, August 29, 2012

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 23፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ምክር ያቋቋሟቸውን ኩባንያዎች ስራ አስፍተው እንደሚቀጥሉ የሜድሮክ ኢትዮጵያ ሊቀመንበር ሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ገለፁ ።



የኩባንያው ሰራተኞች ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል ።

በስነስርዓቱ ላይ የተገኙት ሼክ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለሀዝብ ማሰበን ፣ ህዝብን ማፍቀርንና ለህዝብ መስራትን ያስተማሩኝ መሪ ነበሩ ብለዋል ።

የኢትዮጵያ ህዝብ መሪውን ሲያጣ እኔ ደግሞ ቀኝ እጄን አጥቻለሁ ነው ያሉት ።

በጠቅላይ ሚኒስትሩ እረፍት ያዘነው የኢትዮጵያ ህዝብም ውለታ የማይረሳ መሆኑን መመልከታቸውን ተናግረዋል ።

በአቶ መለስ ምክር ያቋቋምናቸውን ኩባንያዎችንም ስራ በበለጠ አስፍተን አንቀጥላለን እናተም በርቱ ብለዋል የኩባንያውን ሰራተኞች ።

ተግተው በመስራትም የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ራእይ ለማሳካት በሰራተኛው ፊት ሼክ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲን ቃል መግባታቸውን የዘገበው ኤልያስ ተክለውልድ ነው ።

source: www.fanabc.com

No comments:

Ethiopian can not afford a prolonged war.

Ethiopian can not afford a prolonged war. Ethiopia as the poorest country in the world is dependent on aid. A prolonged war simply depletes ...